የሀገር ውስጥ ዜና

ዛሬ ለኢትዮጵያ እና ለኢትዮጵያውያን እጅግ ታሪካዊ ቀን ነው -ፕሬዚዳንት ሣህለወርቅ

By Tibebu Kebede

July 22, 2020

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 15፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) ፕሬዚዳንት ሣህለወርቅ ዘውዴ የህዳሴ ግድቡን የመጀመሪያ ሙሌት መጠናቀቅ በማስመልከት ለኢትዮጵያ ህዝብ የአንኳን ደስ አላችሁ መልዕክት አስተላለፉ።

ፕሬዚዳንቷ ባስተላለፏት መልዕክት ዛሬ ለኢትዮጵያ እና ለኢትዮጵያውያን እጅግ ታሪካዊ ቀን ነው ፤ ህልማችን እውን እየሆነ ነው ብለዋል።