የሀገር ውስጥ ዜና

በደረስንበት የስኬት ምዕራፍ ሳንታጠር፤ ድላችንን እያጣጣምን ለላቀ ድል መነሳት ይኖርብናል- ም/ጠ/ሚኒስትር ደመቀ መኮንን

By Tibebu Kebede

July 23, 2020

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 16፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) በደረስንበት የስኬት ምዕራፍ ሳንታጠር፤ ድላችንን እያጣጣምን ለላቀ ድል መነሳት ይኖርብናል አሉ የኢፌዴሪ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር አቶ ደመቀ መኮንን።

ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር አቶ ደመቀ መኮንን የህዳሴ ግድብ የመጀመሪያ ዙር የውኃ ሙሌት በስኬት በመጠናቀቁ የእንኳን ደስ አላችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል።