አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 16፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) ኢትዮጵያ የአባይ ወንዝን እንዳትጠቀም ይደርስባት የነበረው የፍትህ ማጣት፤ የግድቡ የውሃ ሙሌትን በማከናወን በጋራ ጥረት ታላቅ ገድል ተፈጽሟል አሉ የቀድሞ ጠቅላይ ሚኒስትር አቶ ሀይለማርያም ደሳለኝ።
ከፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት ጋር ቆይታ የነበራቸው የቀድሞ ጠቅላይ ሚኒስትር ጥበብ በተሞላበት የዲፕሎማሲ ጥረት በጋራ በመቆም የውሃ ሙሌቱ መከናወኑ ድል ነው ብለዋል።