የሀገር ውስጥ ዜና

ኮሚሽኑ በኦሮሚያ ክልል በነበረው የፀጥታ ችግር ለተፈናቀሉ ከ7 ሺህ በላይ ሰዎች የዕለት ደራሽ ድጋፍ እያቀረበ ነው

By Tibebu Kebede

July 25, 2020

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 18፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የብሔራዊ አደጋ ስጋት ሥራ አመራር ኮሚሽን በኦሮሚያ ክልል በነበረው የፀጥታ ችግር ለተፈናቀሉ 7 ሺህ 800 ሰዎች የዕለት ደራሽ እርዳታ እያቀረበ መሆኑን ምክትል ኮሚሽነሩ አስታወቁ።

ምክትል ኮሚሽነሩ አቶ ዳመነ ዳሮታ ኮሚሽኑ ከአርቲስት ሐጫሉ ሁንዴሳ ሕልፈት በኋላ በነበረው የፀጥታ ችግር በክልሉ ለተፈናቀሉ ወገኖች ድጋፍ እያቀረበ ነው ብለዋል።