የሀገር ውስጥ ዜና

ፕሬዚዳንት ታዬ የሥራ ጊዜያቸውን ያጠናቀቁትን የጋምቢያ አምባሳደር አሰናበቱ

By ዮሐንስ ደርበው

January 21, 2025

አዲስ አበባ፣ ጥር 13፣ 2017 (ኤፍ ቢ ሲ) ፕሬዚዳንት ታዬ አጽቀ ሥላሴ የሥራ ጊዜያቸውን ያጠናቀቁትን በኢትዮጵያ የጋምቢያ አምባሳደር ጃይናባ ጃግኔን አሰናበቱ፡፡

በኢትዮጵያ እና ጋምቢያ መካከል ያለው ግንኙነት በማጠናከር ረገድ አምባሳደሩ ላበረከቱት ሚና ፕሬዚዳንቱ አመሥግነዋል፡፡

በቀጣይም በሀገራቸው በሚኖራቸው ኃላፊነት የሀገራቱን ግንኙነት በይበልጥ ለማጠናከር በትጋት እንዲሠሩ ጠይቀዋል፡፡