አዲስ አበባ፣ ጥር 14፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) የትምህርት ሚኒስትሩ ብርሃኑ ነጋ (ፕ/ር) በጎንደር ከተማ የሚገኘውን የፋሲል ቤተ-መንግሥት ጎብኝተዋል፡፡
ከሚንስትሩ በተጨማሪ የጎንደር ከተማ አሥተዳደር ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባና የጎንደር ዩንቨርሲቲ ፕሬዚዳንት አስራት አፀደ ወይን (ዶ/ር) እንዲሁም ሌሎች የመንግሥት ሥራ አመራሮች በጉብኝቱ ተሳትፈዋል፡፡
በቅርቡ ጥገና የተደረገለትን የፋሲል ቤተ-መንግሥት የመንግሥት ከፍተኛ አመራሮችን ጨምሮ በርካታ የሀገር ውስጥ እና የውጭ ቱሪስቶች እየጎበኙት ነው፡፡
በሰላም አስመላሽ