የሀገር ውስጥ ዜና

በድንገተኛ ፍተሻ 18 ኩንታል አደንዛዥ ዕጽ ተያዘ

By ዮሐንስ ደርበው

January 24, 2025

አዲስ አበባ፣ ጥር 16፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ሀላባ ዞን ቁሊቶ ከተማ ፖሊስ በሻሸመኔ መግቢያ በኩል ባደረገው ድንገተኛ ፍተሻ 18 ኩንታል አደንዛዥ ዕጽ መያዙን አስታወቀ፡፡

አደንዛዥ ዕጹ በደረቅ ጭነት ተሽከርካሪ ተጭኖ ሲንቀሳቀስ ከሁለት ግለሰቦች ጋር እጅ ከፍንጅ መያዙን የከተማዋ ፖሊስ ጽሕፈት ቤት መረጃ አመላክቷል፡፡