የሀገር ውስጥ ዜና

ጠ/ሚ ዐቢይ (ዶ/ር) በአጋሮ እና በሻሻ የልማት ሥራዎችን ጎበኙ

By ዮሐንስ ደርበው

January 26, 2025

አዲስ አበባ፣ ጥር18፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) እና ቀዳማዊት እመቤት ዝናሽ ታያቸው በአጋሮ እና በሻሻ የተለያዩ የልማት ሥራዎች ጎብኝተዋል፡፡

ከተጎበኙት የልማት ሥራዎች መካከልም÷ የመንገድ፣ ሻይ ቅጠል ልማት እና ችግኝ ማፍያ ጣቢያዎች ይገኙበታል፡፡

በተጨማሪም ትምህርት ቤት፣ የአጋሮ ኮሪደር ሥራ እና የአቮካዶ ዘይት መጭመቂያ የጉብኝቱ መዳረሻ መሆናቸውን የጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት መረጃ አመላክቷል፡፡