የሀገር ውስጥ ዜና

ጠ/ ሚ ዐቢይ በኤሌክትሪክ ኃይል የምትሠራ መኪና በስጦታነት ተበረከተላቸው

By Feven Bishaw

July 27, 2020

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 20፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ በኤሌክትሪክ ኃይል የምትሠራ እና የሀዩንዳይ ኩባንያ አካል በሆነው ማራቶን ሞተርስ ሙሉ በሙሉ በኢትዮጵያ የተገጣጠመች የመጀመሪያ መኪና በስጦታነት ተበረከተላቸው።

ጠቅላይ ሚኒስትሩ ለሀዩንዳይ ፕሬዚዳንት ባቀረቡት ጥያቄ መሠረት፣ በኢትዮጵያ የኤሌክትሪክ መኪናዎችን የመገጣጠም ሥራ ተጀምሯል።