የሀገር ውስጥ ዜና

በመዲናዋ የፓሌቲቭ ኬር አገልግሎት በ22 ጤና ጣቢያዎች እየተሰጠ ነው

By Mikias Ayele

January 29, 2025

አዲስ አበባ፣ ጥር 21፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) በአዲስ አበባ በሕክምና ማዳን የማይቻሉ ሕመሞችን ስቃይ ለመቀነስ የሚሰጠው አገልግሎት (ፖሌቲቭ ኬር) በ22 ጤና ጣቢያዎች እየተሰጠ መሆኑን የከተማዋ ጤና ቢሮ አስታውቋል፡፡

የቢሮው ም/ሃላፊ ዶ/ር ሙሉጌታ እንዳለ እንደገለጹት÷በሕክምና ማዳን የማይቻሉ ሕመሞች እያደረሱት ያለውን ስቃይ መቀነስ የሚያስችል አገልግሎት ከባለፈው ዓመት ጀምሮ በጤና ተቋማት እየተሰጠ ነው ።

በዚህም 22 ጤና ጣቢያዎችን ከሆስፒታሎች ጋር በማስተሳሰር ዜጎች በጤና ተቋማት አልጋ ይዘው፣ በምልልስ አሊያም ቤታቸው ሆነው አገልግሎቱን እንዲያገኙ እየተደረገ ነው ብለዋል፡፡

ዘርፉ አሰራር ተዘርግቶለት በየጊዜው እየተገመገመ መሆኑን ጠቁመው÷ በተጓዳኝ የሥነ-ልቦና ሕክምና አገልግሎት  እየተሰጠ እንደሚገኝ ጠቁመዋል፡፡

የአገልግሎት ፈላጊዎችን ቁጥር ግምት ውስጥ በማስገባት ሕክምናውን የሚሰጡ ጤና ተቋማትን ቁጥር ለማሳደግ እንደሚሰራም አስረድተዋል፡፡

በመሳፍንት እያዩ