አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 20፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) በኢትዮጵያ ባለፉት 24 ሰዓታት ለ7 ሺህ 9 ሰዎች የላቦራቶሪ ምርምራ ተደርጎ 579 ሰዎች ቫይረሱ እንደተገኘባቸው የጤና ሚኒስትር ዶክተር ሊያ ታደሰ አስታወቁ።
በዚህም በኢትዮጵያ በቫይረሱ የተያዙ ሰዎች ቁጥር 14 ሺህ 547 ሰዎች የደረሰ ሲሆን ከእነዚህ መካከል ቫይረሱ ያለባቸው 7 ሺህ 931 ሰዎች የህክምና ክትትል እየተደረገላቸው ይገኛል ብለዋል።