የሀገር ውስጥ ዜና

ባለፉት 24 ሰዓታት 579 ሰዎች የኮሮና ቫይረስ ሲገኝባቸው የ5 ሰዎች ህይወት አልፏል

By Feven Bishaw

July 27, 2020

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 20፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) በኢትዮጵያ ባለፉት 24 ሰዓታት ለ7 ሺህ 9 ሰዎች የላቦራቶሪ ምርምራ ተደርጎ 579 ሰዎች ቫይረሱ እንደተገኘባቸው የጤና ሚኒስትር ዶክተር ሊያ ታደሰ አስታወቁ።

በዚህም በኢትዮጵያ በቫይረሱ የተያዙ ሰዎች ቁጥር 14 ሺህ 547 ሰዎች የደረሰ ሲሆን ከእነዚህ መካከል ቫይረሱ ያለባቸው 7 ሺህ 931 ሰዎች የህክምና ክትትል እየተደረገላቸው ይገኛል ብለዋል።