የሀገር ውስጥ ዜና

ርዕሰ መሥተዳድር ጥላሁን ለብልጽግና ፓርቲ ፕሬዚዳንት የእንኳን ደስ አለዎት መልዕክት አስተላለፉ

By ዮሐንስ ደርበው

February 02, 2025

አዲስ አበባ፣ ጥር 25፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መሥተዳድር ጥላሁን ከበደ ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የብልጽግና ፓርቲ ፕሬዚዳንት ሆነው በድጋሚ መመረጣቸውን ተከትሎ የእንኳን ደስ አለዎት መልዕክት አስተላልፈዋል፡፡

የብልጽግና ፓርቲ ሁለተኛ መደበኛ ጉባዔ ዐቢይ አሕመድን (ዶ/ር) የፓርቲው ፕሬዚዳንት አድርጎ መርጧል።

ይህንን ተከትሎም ርዕሰ መሥተዳድሩ ባስተላለፉት የመልካም ምኞት መልዕክት÷ ለፓርቲው ፕሬዚዳንት መልካም የሥራ ዘመን ተመኝተዋል።