የሀገር ውስጥ ዜና

መርማሪ ፖሊስ በአቶ ጃዋር መሃመድ ቤት በግለሰብ እጅ የማይገኙ ሳተላይቶችና ከውጭ በድብቅ የገቡ ኤሌክትሮኒክስ መሳሪያዎች ማግኘቱን ገለጸ

By Tibebu Kebede

July 29, 2020

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 22፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የፌዴራል መርማሪ ፖሊስ በአቶ ጃዋር መሃመድ ቤት በድጋሚ ባደረገው ፍተሻ በግለሰብ እጅ የማይገኙ ሳተላይቶችና ከውጭ በድብቅ የገቡ ኤሌክትሮኒክስ መሳሪያዎችን ማግኘቱን ገለጸ።

መርማሪ ፖሊስ ሃምሌ 9 ቀን 2012 ዓ.ም በፍርድ ቤቱ በተሰጠው የ13 ቀን ተጨማሪ ጊዜ የሰራውን አዳዲስ የምርመራ ስራዎችን ይፋ አድርጓል።