የሀገር ውስጥ ዜና

ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ ዳሬ ሰላም ገቡ

By ዮሐንስ ደርበው

February 21, 2025

አዲስ አበባ፣ የካቲት 14፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ ታንዛኒያ ዳሬ ሰላም ገብተዋል።

አቶ ተመስገን ወደ ዳሬ ሰላም ያቀኑት ለ3ኛ ጊዜ በሚካሔደው የጂ-25 የአፍሪካ ቡና አምራች ሀገራት ጉባዔ ላይ ለመካፈል ነው፡፡

በጉባዔው ላይ የአህጉሩ ቀዳሚ ቡና አምራች የሆነችው ኢትዮጵያን ጨምሮ፤ 25 የአፍሪካ ቡና አምራች ሀገራት እንደሚሳተፉ ተገልጿል፡፡

”የአፍሪካ የቡና ኢንዱስትሪን በማነቃቃት ለወጣቶች የሥራ ዕድሎችን መክፈት” በሚል መሪ ሐሳብ ነው ጉባዔው የሚካሄደው፡፡

በጉባዔው ላይ ዘርፉን ለማነቃቃትና ሰፊ የሥራ ዕድል ለመፍጠር የሚያስችሉ ውይይቶች እንደሚደረጉ ይጠበቃል፡፡