የሀገር ውስጥ ዜና

ፕሬዚዳንት ታዬ በናሚቢያ የቀድሞ ፕሬዚዳንት ሕልፈት የተሰማቸውን ሃዘን ገለጹ

By Melaku Gedif

February 27, 2025

አዲስ አበባ፣ የካቲት 20፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) የኢፌዲሬ ፕሬዚዳንት ታዬ አጽቀ ሥላሴ በናሚቢያ የቀድሞ ፕሬዚዳንት ሳም ኑጆማ ሕልፈት የተሰማቸውን ሃዘን ገለጹ።

ፕሬዚዳንት ታዬ በጽሑፍ ባስተላለፉት የሃዘን መግለጫ÷ የቀድሞ ፕሬዚዳንት ሳም ኑጆማ ናሚቢያን “መካከለኛ ገቢ ወዳለው ሀገር ያሻገሩ መሪ ተብለው ይታወሳሉ” ሲሉ አስፍረዋል።

ፕሬዚዳንት ታዬ አክለውም ሳም ኑጆማ የናሚቢያ መስራች አባት እና ሀገራቸውን የቀየሩ መሪ ነበሩ ማለታቸውን የፕሬዚዳንት ጽ/ቤት መረጃ ያመለክታል።