አዲስ አበባ፣ የካቲት 21፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) በስልጤ ዞን ወራቤ ከተማ አሥተዳደር 01 ቀበሌ ዳሎቻ ማዞሪያ አካባቢ በደረሰ የትራፊክ አደጋ የሁለት ሰዎች ሕይዎት አለፈ፡፡
አደጋው የተከሰተው ዛሬ ከጠዋቱ 2 ሠዓት ገደማ መሆኑን የዞኑ ኮሙኒኬሽን መምሪያ መረጃ አመላክቷል፡፡
ከአዲስ አበባ ወደ ሆሳዕና ሲጓዝ የነበረ የደረቅ ጭነት ተሽከርካሪ በመገልበጡ የተከሰተ አደጋ መሆኑም ነው የተገለጸው፡፡