የሀገር ውስጥ ዜና

የአረፋ በዓልን ስናከብር ራሳችንን ከኮቪድ-19 ወረርሽኝ በመጠበቅ ሊሆን ይገባል- ጤና ሚኒስቴር

By Tibebu Kebede

July 30, 2020

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 23፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) ህዝበ ሙስሊሙ የኢድ-አልአድሃ በዓልን ሲያከብር ዓለም አቀፍ ወረርሽኝ ከሆነው የኮሮናቫይረስ ራሱን በመጠበቅ ሊሆን እንደሚገባ የጤና ሚኒስትሯ ዶክተር ሊያ አሳሰቡ።

የጤና ሚኒስትሯ ዶክተር ሊያ ታደሰ በነገው ዕለት የሚከበረውን የአረፋ በዓልን አስመልክተው የእንኳን አደረሳችሁ እና ለኮቪድ-19 ሊደረግ ስለሚገባው ጥንቃቄ መልእክት አስተላልፈዋል።