የሀገር ውስጥ ዜና

የተለያዩ የሕብረተሰብ ክፍሎች አዲስ ኢንተርናሽናል ኮንቬንሽን ማዕከልን ጎበኙ

By Melaku Gedif

March 05, 2025

አዲስ አበባ፣ የካቲት 26፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) የተለያዩ የሕብረተሰብ ክፍሎች አዲስ ኢንተርናሽናል ኮንቬንሽን ማዕከልን ጎብኝተዋል፡፡

በጉብኝት መርሐ ግብሩ የሃይማኖት አባቶች፣ አባ ገዳዎች፣ ሀደ ሲንቄዎች እና ነዋሪዎች መሳተፋቸውን የከንቲባ ጽ/ቤት መረጃ ያመላክታል።

የጉብኝቱ ተሳታፊዎች መንግሥት መሰል ሁለንተናዊ ፋይዳ ያላቸው መሰረተ ልማቶችን እየገነባ በመሆኑ ያላቸውን አድናቆት ገልፀዋል፡፡

ማዕከሉ የቱሪዝም ፍሰትን በማሳለጥ የኢትዮጵያን ገቢ ማሳደግ እንደሚችልም ነው የተናገሩት፡፡