የሀገር ውስጥ ዜና

“መለኮታዊ ጉብኝት ለኢትዮጵያ” መንፈሳዊ መርሐ-ግብር መካሄድ ጀመረ

By Mikias Ayele

March 08, 2025

አዲስ አበባ፣ የካቲት 29፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) “መለኮታዊ ጉብኝት ለኢትዮጵያ” መንፈሳዊ መርሐ-ግብር በመስቀል ዐደባባይ መካሄድ ጀመሯል፡፡

መርሐ-ግብሩን ያዘጋጁት የኢትዮጵያ ወንጌል አማኞች አብያተ ክርስቲያናት ካውንስል ከቢሊ ግራሃም የወንጌል ማኅበር ጋር በመተባበር ነው፡፡

እየተካሄደ የሚገኘው መርሐ-ግብር፤ የጸሎት፣ የወንጌል ስብከት እና የዝማሬ ፕሮግራምን ያካተተ ነው ተብሏል፡፡

የኢትዮጵያ የወንጌል አማኞች አብያተክርስቲያናት ካውንስል ጠቅላይ ፀሐፊ ቄስ ደረጀ ጀምበሩ፤ መርሐ-ግብሩን በፀሎት አስጀምረውታል።

ከ1 ሺህ 600 በላይ አብያተ ክርስቲያናት ከቢሊ ግራሃም የወንጌል ማኅበር ጋር በመተባበር በመለኮታዊ ጉብኝት ላይ ተሳታፊ ናቸው ።

በመርሐ-ግብሩ ላይ በርካታ ምዕመናን ተገኝተዋል።

በበረከት ተካልኝ ፣ ሰለሞን በየነ እና ዘረዓያዕቆብ ያዕቆብ