የሀገር ውስጥ ዜና

ለአምባሳደር ምስጋኑ አርጋና ለአምባሳደር ሱለይማን ደደፎ የባለሙሉ ስልጣን አምባሳደርነት ሹመት ተሰጠ

By Mikias Ayele

March 10, 2025

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 1፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) የኢፌዴሪ ፕሬዚዳንት ታዬ አጽቀ ሥላሴ ለአምባሳደር ምስጋኑ አርጋ እና ለአምባሳደር ሱለይማን ደደፎ የባለሙሉ ስልጣን አምባሳደርነት ሹመት ሰጥተዋል፡፡

ፕሬዚዳንት ታዬ በሕገመንግስቱ አንቀጽ 71 ንዑስ አንቀጽ 3 መሰረት ለሁለት የመንግስት ከፍተኛ የሥራ ሃላፊዎች የባለሙሉ ስልጣን አምባሳደርነት ሹመት መስጠታቸውን የፕሬዚዳንት ጽ/ቤት መረጃ አመላክቷል፡፡