የሀገር ውስጥ ዜና

አቶ አረጋ ከበደ የተለያዩ ሹመቶችን ሰጡ

By ዮሐንስ ደርበው

March 28, 2025

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 19፣2017 (ኤፍ ኤም ሲ) የአማራ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ አረጋ ከበደ የተለያዩ ሹመቶችን ሰጥተዋል።

በዚህ መሠረት ዶ/ር እሸቱ የሱፍ የክልሉ ሠላምና ፀጥታ ቢሮ ኃላፊ፣ ኮሚሸነር ዘላለም መንግስቴ የፖሊስ ኮሚሽን ኮሚሽነር እንዲሁም አቶ አስቻለ አላምሬ የሚሊሻ ጽህፈት ቤት ኃላፊ ሆነው መሾማቸውን የአማራ ኮሙኒኬሽን መረጃ ያመላክታል፡፡