የሀገር ውስጥ ዜና

በ10 ዓመት የልማት እቅዱ በባቡር ትራንስፖርት ዘርፍ ኢትዮጵያን ከምስራቅ አፍሪካ ቀዳሚ ለማድረግ መታቀዱ ተገለፀ

By Tibebu Kebede

August 05, 2020

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 29፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የትራንስፖርት ሚኒስቴር ተጠሪ ተቋማት የሆኑት የማሪታይም ጉዳዮች ባለስልጣን፣ የፌዴራል ትራንስፖርት ባለስልጣን እና የኢትዮ ጅቡቲ ባቡር አክስዮን ማህበር የ10 ዓመት የልማት እቅዳቸውን አቅርበው ውይይት ተደረጎበታል፡፡

በውይይቱም የማሪታይም ጉዳዮች ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር አቶ መኮንን አበራ ደረቅ ወደብን ማልማት ለሃገር ውስጥ የግል ዘርፍ የተተወ ብቻ ሳይሆን ለውጭ ባለሃብቶችም ክፍት መሆኑን ተናግረዋል።