የሀገር ውስጥ ዜና

የክልሉን ሰላም ለማደፍረስ የሚሰሩ አካላትን እንደሚታገሉ የአርሲ ዞን ወጣቶች ገለጹ

By Tibebu Kebede

August 05, 2020

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 29፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የጸረ-ሰላም ኃይሎችን ተልዕኮ ለማስፈጸም ሲባል የክልሉን ሰላም ለማደፍረስ የሚሰሩ አካላትን እንደሚታገሉ የአርሲ ዞን ወጣቶች ገለጹ።

ወጣቶቹ የአካባቢውን ዘላቂ ሰላም በማስጠበቅ ዙሪያ ከፌዴራልና ከክልሉ አመራሮች ጋር በአሰላ ከተማ እየተወያዩ ነው።