አዲስ አበባ ፣ሐምሌ 29 ፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) ጠቅላይ ሚኒስር ዐቢይ አህመድ አሜሪካ ለኢትዮጵያ ላበረከተችው የመተንፈሻ ቬንትሌተሮች ድጋፍ ምስጋና አቀረቡ።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ በፌስቡክ ገፃቸው ላይ ኢትዮጵያ የኮቪድ 19ን ወረርሽኝ ለመከላከል የምታደርገውን ጥረት ለማገዝ ከፍተኛ ጥራት ያላቸውን 250 የመተንፈሻ ቬንትሌተሮች እና ሌሎች ወሳኝ የሕክምና መገልገያዎች ድጋፍ ስላደረጉልን፣ የዩናይትድ ስቴትስ መንግሥትን አመሰግናለሁ ብለዋል።