የሀገር ውስጥ ዜና

በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ዛሬ ሁለት ተጠባቂ ጨዋታዎች ይካሄዳሉ

By Mikias Ayele

April 12, 2025

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 4፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) በ32ኛ ሳምንት የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ማንቼስተር ሲቲ ከክሪስታል ፓላስ እንዲሁም አርሰናል ከብሬንትፎርድ የሚያደርጉት ጨዋታ ይጠበቃል፡፡

ቀን 8 ሰዓት ከ30 በሚደረገው የሳምንቱ የመክፈቻ ጨዋታ ማንቼስተር ሲቲ ክሪስታል ፓላስን በሜዳው የሚያስተናግደበት ጨዋታ ተጠባቂ ነው፡፡

መርሐ ግብሩ ሲቀጥል ቀን 11 ሰዓት ላይ ሶስት ጨዋታዎች የሚደረጉ ሲሆን÷በዚህም ብራይተን ከሌስተር ሲቲ፣ ኖቲንግሃም ፎረስት ከኤቨርተን እንዲሁም ሳውዝሃምፕተን ከአስቶንቪላ ይገናኛሉ፡፡

በቅዳሜ ጨዋታዎች ማጠናቀቂያ ምሽት1 ሰዓት ከ30 ላይ አርሰናል በኤሚሬትስ ስታዲየም ብሬንትፎሮድን የሚያስተናግድ ይሆናል፡፡