የሀገር ውስጥ ዜና

የአማራ ክልል ኢንዱስትሪና ኢንቨስትመንት ቢሮ 153 ቢሊየን ብር ካፒታል ላስመዘገቡ ባለሀብቶች የኢንቨስትመንት ፈቃድ ሰጠ

By Meseret Demissu

August 06, 2020

አዲስ አበባ ፣ ሐምሌ 30 ፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የአማራ ክልል ኢንዱስትሪና ኢንቨስትመንት ቢሮ 153 ቢሊየን ብር ካፒታል ላስመዘገቡ ባለሃብቶች የኢንቨስትመንት ፍቃድ መስጠቱን አስታወቀ።

የክልሉ ኢንዱስትሪና ኢንቨስትመንት ቢሮ የህዝብ ግንኙነት ዳይሬክተር አቶ ይኸነው ዓለም ÷ በ2012 በጀት ዓመት ለ2 ሺህ 214 ባለሀብቶች ፍቃድ ለመስጠት ታቅዶ ለ2 ሺህ 908 ባለሀብቶች ፍቃድ መሠጠቱን ተናግረዋል።