አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 18፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) ግሪክ በተለያዩ የሙያ ዘርፎች የሚሰማራ የሰለጠነ የሰው ሀይል አቅርቦት ላይ ከኢትዮጵያ ጋር በትብብር መስራት እንደምትፈልግ ገለጸች
የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ዴኤታ ተሻለ በሬቻ (ዶ/ር) ከግሪክ ልዑካን ቡድን ጋር ተወያይተዋል፡፡
በውይይታቸውም በሁለቱ ሀገራት ህጋዊ የሰለጠነ የሰው ሀይል ስምሪት ማድረግ በሚቻልበት ሁኔታ መክረዋል፡፡
ግሪክ በተለያዩ የሙያ ዘርፎች የሚሰማራ የሰለጠነ የሰው ሀይል አቅርቦት ላይ ከኢትዮጵያ ጋር በትብብር መስራት እንደምትፈልግ ልዑካኑ መግለጻቸውን የሚኒስቴሩ መረጃ አመልክቷል፡፡