የሀገር ውስጥ ዜና

የደቡብ ክልል ምክር ቤት መደበኛ ጉባኤውን ማካሄድ ጀመረ

By Feven Bishaw

August 07, 2020

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ1፣2012 ( ኤፍ.ቢ.ሲ) የደቡብ ክልል ምክር ቤት 5ኛ ዙር 5ኛ አመት የስራ ዘመን 11ኛ መደበኛ ጉባኤ በሀዋሳ መካሄድ ጀምሯል።

የምክር ቤቱ አፈ ጉባኤ ወይዘሮ ሄለን ደበበ የዘመናት የህዝቦች ጥያቄና ቁጭት የሆነው የታላቁ ህዳሴ ግድብ ወደ ውጤት መቃረብና የመጀመሪያ ሙሌት በስኬት በመጠናቀቁ እንኳን ደስ አላችሁ ብለዋል።