የሀገር ውስጥ ዜና

በኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ 625 ኢንዱስትሪዎች ዳግም ሥራ ጀመሩ

By Mikias Ayele

May 03, 2025

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 25፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) በኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ 625 ተዘግተው የነበሩ አምራች ኢንዱስትሪዎች ወደ ሥራ መግባታቸውን የአምራች ኢንዱስትሪ ልማት ኢንስቲትዩት አስታውቋል፡፡

የኢንስቲትዩቱ ዋና ዳይሬክተር ሚልኬሳ ጃጋማ (ዶ/ር) ለፋና ሚዲያ ኮርፖሬሽን እንዳሉት÷በንቅናቄው የኢንዱስትሪዎችን የማምረት አቅም ከ46 በመቶ ወደ 61 በመቶ ከፍ ማድረግ ተችሏል፡፡

በበጀት ዓመቱ ባለፉት ዘጠኝ ወራት 3 ነጥብ 1 ቢሊየን ብር ዋጋ ያላቸው ተኪ ምርቶች መመረታቸውን አመልክተዋል፡፡

በዚህም ከፍተኛ የውጪ ምንዛሪ ማዳን መቻሉን ገልጸው÷ንቅናቄው ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ተናግረዋል፡፡

ከዛሬ ጀምሮ የሚከፈተው 3ኛው የኢትዮጵያ ታምርት ዓለም አቀፍ ኤክስፖ እስካሁን በንቅናቄው የተገኙ ውጤቶችን ወደ ላቀ ደረጃ ለማድረስ እንደሚያግዝ ጠቅሰዋል፡፡

በዙፋን ካሳሁን