አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 30፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) በአዲስ አበባ ከተማ የኩፍኝ በሽታ መከላከያ ክትባት ከሚቀጥለው ሳምንት ጀምሮ እንደሚሰጥ የከተማ አስተዳደሩ ጤና ቢሮ አስታወቀ።
የክትባት ዘመቻው ከግንቦት 6 እስከ 15 ቀን 2017 ዓ.ም የሚካሄድ መሆኑ ተገልጿል።
የጤና ቢሮው ለፋና ሚዲያ ኮርፖሬሽን እንደገለፀው፤ በክትባት ዘመቻው ዕድሜያቸው ከ9 ወር እስከ 5 ዓመት የሆኑ ከግማሽ ሚሊየን በላይ ህፃናት ይከተባሉ።
ከ3 ሺህ 400 በላይ ባለሙያዎች በክትባት ዘመቻው ይሳተፋሉ ብሏል፡፡
በክትባት ዘመቻው የኩፍኝ ክትባትን ጨምሮ ሌሎች የቫይታሚን ኤ ጠብታ እና የአንጀት ትላትል መድሃኒት ይሰጣል ተብሏል፡፡
በሲፈን መኮንን