ስፓርት

54ኛው የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ሻምፒዮና ተጠናቀቀ

By Mikias Ayele

May 11, 2025

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 3፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) በኢትዮጵያ ስፖርት አካዳሚ ሲካሄድ የቆየው 54ኛው የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ሻምፒዮና በድምር ውጤት በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ አሸናፊነት ተጠናቅቋል።

በሻምፒዮናው በድምር ውጤት ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በ279 ነጥብ አንደኛ ደረጃን ይዞ ሲያጠናቅቅ፣ መቻል በ242 ነጥብ ሁለተኛ እንዲሁም ሸገር ሲቲ በ143 ነጥብ ሶስተኛ ደረጃ በመያዝ አጠናቀዋል።

በሻምፒዮናው 1 ሺህ 379 አትሌቶች፣ 31 ክለቦችና ተቋማት እንዲሁም ክልሎችና ከተማ አስተዳደሮች ተሳትፈዋል።

በሻምፒዮናው ማጠቃለያ ሥነ ሥርዓት ላይ የባህልና ስፖርት ሚኒስትር ዲኤታ ረዳት ፕሮፌሰር ነብዩ ባዬ፣ የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ፕሬዚዳንት ኮማንደር አትሌት ስለሺ ስህንን ጨምሮ የፌደሬሽኑ አመራሮች እና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።