የሀገር ውስጥ ዜና

ኢትዮጵያ ቡና እና ወልዋሎ ዓዲግራት ዩኒቨርሲቲ አቻ ተለያዩ

By Mikias Ayele

May 29, 2025

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 21፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) በ32ኛ ሳምንት የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ መርሐ ግብር ኢትዮጵያ ቡና እና ወልዋሎ ዓዲግራት ዩኒቨርሲቲ በአቻ ውጤት ተለያተዋል፡፡

ቀን 9 ሰዓት ላይ በአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም የተደረገው ጨዋታ ግብ አልተቆጠረበትም።

ቀደም ሲል ዛሬ ረፋድ 3:30 ላይ በተካሄደ ጨዋታ አዳማ ከተማ ሀድያ ሆሳዕናን በረከት ወ/ዮሐንስ (በራስ ላይ) ባስቆጠራት ግብ 1 ለ 0 ማሸነፉ ይታወሳል።

የ32ኛ ሳምንት የጨዋታ መርሐ ግብር ምሽት 12 ሰዓት ላይ ቀጥሎ ሲካሄድ ወላይታ ድቻ ከኢትዮ ኤሌክትሪክ ይገናኛሉ።