ስፓርት

ሀዋሳ ከተማ መቻልን አሸነፈ

By Adimasu Aragawu

May 31, 2025

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 23፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) በ32ኛ ሳምንት የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ መርሐ ግብር ሀዋሳ ከተማ መቻልን 3 ለ 1 አሸንፏል።

የሀዋሳ ከተማን ማሸነፊያ ግቦች አሊ ሱሌማን፣ ተባረክ ሄፋሞ እና አቤኔዘር ዮሐንስ አስቆጥረዋል።

መቻልን ከመሸነፍ ያልታደገውን ብቸኛ ግብ ምንይሉ ወንድሙ በፍጹም ቅጣት ምት አስቆጥሯል።

በአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም እየተካሄደ የሚገኘው የሊጉ መርሐ ግብር ሲቀጥል ምሽት 12:00 ላይ መቐለ 70 እንደርታ ከፋሲል ከነማ ይገናኛሉ።