የሀገር ውስጥ ዜና

የፌደራል ተቋማት እና ማኅበራት አጀንዳቸውን ለኮሚሽኑ አስረከቡ

By ዮሐንስ ደርበው

June 01, 2025

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 24፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) የፌደራል ተቋማት እና ማኅበራት አጀንዳቸውን ለሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን አስረከቡ።

ተቋማቱ ዛሬን ጨምሮ ላለፉት ሦስት ቀናት በአጀንዳ ማሰባሰብ ምክክር ላይ ነበሩ፡፡

በዛሬው ዕለትም አጀንዳዎቻቸውን ለዋና ኮሚሽነር መስፍን አርዓያ (ፕ/ር)፣ ለምክትል ዋና ኮሚሽነር ሂሩት ገብረሥላሴ እና ኮሚሽነር አምባዬ ኡጋቶ (ዶ/ር) አስረክበዋል።

በይስማው አደራው