የሀገር ውስጥ ዜና

አሰባሳቢ ትርክቶችን ይበልጥ ለማስረጽ የጋራ ማንነት ግንባታ ላይ በትኩረት መስራት ይገባል – ቢቂላ ሁሪሳ (ዶ/ር)

By Melaku Gedif

June 12, 2025

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 5፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) የሚዲያና የኮሙኒኬሸን ባለሙያዎች አሰባሳቢ ትርክቶችን ለማስረጽ በትኩረት መስራት ይጠበቅባቸዋል አሉ በብልጽግና ፓርቲ የሕዝብና ዓለም አቀፍ ግንኙነት ዘርፍ ኃላፊ ቢቂላ ሁሪሳ (ዶ/ር)።

”የድህረ እውነት ዘመንን በእውቀትና በእውነት” በሚል መሪ ሀሳብ ለአፋር ክልል አመራሮችና የሚዲያና የኮሙኒኬሽን ባለሙያዎች በሰመራ ስልጠና እየተሰጠ ነው።

ቢቂላ ሁሪሳ (ዶ/ር) በዚህ ወቅት÷ ባለፉት ሰባት የለውጥ ዓመታት አሰባሳቢ ትርክቶችን በማስረጽ እንዲሁም የጋራ በሆኑ ማንነቶች ላይ ትኩረት በማድረግ ሲሰራ ቆይቷል ብለዋል።

በዚህም ህብረ ብሔራዊ ለሆነው የአንድነት ጉዞ የጸና መሰረት ማኖር መቻሉን ጠቁመው÷ በድህረ እውነት ዘመን የጋራ ወንድማማችነትን በሚያሳደጉ ጉዳዮች ላይ ማተኮር እንደሚገባ ተናግረዋል፡፡

የሚዲያና የኮሙኒኬሽን ባለሙያዎች በለውጡ ዓመታት የተገኙ ውጤቶችን አጠናክረው ማስቀጠል እንደሚገባቸው ማሳሰባቸውን የዘገበው ኢዜአ ነው።

በብልጽግና ፓርቲ የአፋር ክልል ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ሃላፊ አቶ መሐመድ ሁሴን በበኩላቸው ÷ ባለፉት ሰባት ዓመታት ህብረ ብሔራዊ አንድነትን የማጠናከር ሥራ መከናወኑን አስታውሰዋል፡፡

የሚዲያና የኮሙኒኬሸን ባለሙያዎች የጋራ ትርክትን ማስረጽ ላይ በትብብር እና በትኩረት ሊሰሩ እንደሚገባም አስገንዝበዋል።

ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት፡-

YouTube www.youtube.com/@fanamediacorporation Facebook www.facebook.com/fanabroadcasting Telegram t.me/fanatelevision Website www.fanamc.com TikTok www.tiktok.com/@fana_television WhatsApp www.whatsapp.com/channel/0029VbB0dRxG8l59MUkoWR29 Amharic Entertainment YouTube www.youtube.com/@fanaentertainment Facebook www.facebook.com/wmccwaltamediaandcommunicationcorporate TikTok www.tiktok.com/@fanamc_entertainment Amharic Documentary YouTube www.youtube.com/@fanamcdocumentary በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡ ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስለሆኑ እናመሰግናለን!