ስፓርት

ሲዳማ ቡና እና ድሬዳዋ ከተማ አቻ ተለያዩ

By Adimasu Aragawu

June 12, 2025

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 5፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) በ34ኛ ሳምንት የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ መርሐ ግብር ሲዳማ ቡና እና ድሬዳዋ ከተማ 1 ለ 1 በሆነ አቻ ውጤት ተለያይተዋል።

ቀን 9 ሰዓት በአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም በተካሄደው ጨዋታ ሀቢብ ከማል በፍጹም ቅጣት ምት በ45ኛው ደቂቃ ቀዳሚውን ግብ ለድሬዳዋ ከተማ ሲያስቆጥር÷ ሲዳማ ቡናን አቻ ያደረጋትን ግብ ሀብታሙ ታደሰ በ54ኛው ደቂቃ ማስቆጠር ችሏል።

የሊጉ መርሐ ግብር ሲቀጥል ምሽት 12 ሰዓት ወላይታ ድቻ እና ባህር ዳር ከተማ ይገናኛሉ።