ስፓርት

ሊቨርፑል ፍሎሪያን ቪርትስን ከባየር ሊቨርኩሰን አስፈረመ

By Abiy Getahun

June 20, 2025

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 13፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) ሊቨርፑል ጀርመናዊውን የአጥቂ አማካይ ፍሎሪያን ቪርትስ የክለቡ የዝውውር ክብረ ወሰን በሆነ ዋጋ ከባየር ሊቨርኩሰን ማስፈረሙን ይፋ አድርጓል።

ሊቨርፑል ለተጫዋቹ ዝውውር 100 ሚሊየን ፓውንድ እና ተጨማሪ 16 ሚሊየን ፓውንድ የሚከፍል ሲሆን፥ ለአምስት አመት በአንፊልድ የሚያቆየውን ውል ፈርሟል።

ፍሎሪያን ቪርትስ ለቡንደስሊጋው ክለብ ባየር ሊቨርኩሰን 197 ጨዋታዎችን በማድረግ 57 ግቦችን አስቆጥሯል።

የ22 አመቱ ቪርትስ ለቀዮቹ ፊርማውን ካኖረ በኋላ በሰጠው አስተያየት፥ ለረዥም ጊዜ ስጠብቀው የነበረው ዝውውር በመሳካቱ ደስተኛ ነኝ ብሏል።

በኃይለማርያም ተገኝ

ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት፡-

YouTube www.youtube.com/@fanamediacorporation Facebook www.facebook.com/fanabroadcasting Telegram t.me/fanatelevision Website www.fanamc.com TikTok www.tiktok.com/@fana_television WhatsApp www.whatsapp.com/channel/0029VbB0dRxG8l59MUkoWR29 Amharic Entertainment YouTube www.youtube.com/@fanaentertainment Facebook www.facebook.com/wmccwaltamediaandcommunicationcorporate TikTok www.tiktok.com/@fanamc_entertainment Amharic Documentary YouTube www.youtube.com/@fanamcdocumentary በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡ ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስለሆኑ እናመሰግናለን!