የሀገር ውስጥ ዜና

የአካባቢ ብክለትን ለመከላከል ሁሉም የበኩሉን ሊወጣ ይገባል

By Adimasu Aragawu

June 21, 2025

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 14፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) የአካባቢ ብክለትን ለመከላከል ሁሉም የበኩሉን ሊወጣ ይገባል አሉ የኢፌዲሪ አካባቢ ጥበቃ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ሌሊሴ ነሜ፡፡

“ጽዱ ኢትዮጵያን ባህል ማድረግ” በሚል መሪ ሃሳብ ሁለተኛው ዙር አስተዳደር አቀፍ የአካባቢ ብክለት መከላከል ንቅናቄ ማስጀመሪያ መርሐ ግብር በድሬዳዋ ተካሂዷል፡፡

ዋና ዳይሬክተሯ በዚህ ወቅት÷ የአካባቢ ብክለት አሁን ላለው የጤና እክል ዋነኛ መንስኤ መሆኑን ገልጸው፤ ብክለቱን ለመከላከል ሁሉም የበኩሉን ሊወጣ ይገባል ብለዋል።

የድሬዳዋ አስተዳደር ከንቲባ ከድር ጁሀር በበኩላቸው÷ የአየር ንብረት ለውጥ በዓለም ላይ ተጽዕኖ እያሳደረ ባለበት በዚህ ወቅት ለአካባቢ ጥበቃና ለጽዱ ኢትዮጵያ ልዩ ትኩረት መሰጠቱን አንስተዋል፡፡

አረንጓዴ አሻራ ለድሬዳዋ ከተማ የህልውና ጉዳይ መሆኑንም ጠቁመዋል፡፡

በምንያህል መለሰ

ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት፡-

YouTube www.youtube.com/@fanamediacorporation Facebook www.facebook.com/fanabroadcasting Telegram t.me/fanatelevision Website www.fanamc.com TikTok www.tiktok.com/@fana_television WhatsApp www.whatsapp.com/channel/0029VbB0dRxG8l59MUkoWR29 Amharic Entertainment YouTube www.youtube.com/@fanaentertainment Facebook www.facebook.com/wmccwaltamediaandcommunicationcorporate TikTok www.tiktok.com/@fanamc_entertainment Amharic Documentary YouTube www.youtube.com/@fanamcdocumentary በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡ ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስለሆኑ እናመሰግናለን!