የሀገር ውስጥ ዜና

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) ከጤና ባለሙያዎች ጋር ተወያዩ

By Adimasu Aragawu

June 21, 2025

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 14፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከጤና ባለሙያዎች ጋር ተወያይተዋል።

ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማኅበራዊ ትስስር ገፃቸው ባሰፈሩት መረጃ፥ ከተለያዩ ባለድርሻ አካላት ጋር የምናደርገውን ውይይት በመቀጠል ዛሬ ከጤና ባለሙያዎች ጋር ውይይት አድርገናል ብለዋል።

በውይይቱም እድሎችን እና በጎ ርምጃዎችን ብሎም ክፍተቶችን እና ተግዳሮቶችን ዳሰናል ነው ያሉት።