ቢዝነስ

በጎንደር በ185 ሚሊየን ብር ወጪ የተገነባው የአርቲስት እንየ ታከለ የባህል ምሽት ቤት

By Adimasu Aragawu

June 21, 2025

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 14፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) በ185 ሚሊየን ብር ወጪ በአርቲስት እንየ ታከለ የተገነባውና የጎንደርን ታሪክ የሚመጥን የባህል ምሽት ቤት ተመርቋል።

የባህል ምሽት ቤቱን በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የጎንደር ከተማ አስተዳደር ኢንዱስትሪና ኢንቨስትመንት መምሪያ ኃላፊ አቶ ግርማይ ልጅ ዓለምና የክልል ሥራ ኃላፊዎች መርቀው ከፍተዋል።

በጎንደር ከተማ በርካታ ሆቴሎች ቢኖሩም ደረጃውን የጠበቀ ለእንግዶች አገልግሎት መስጠት የሚችል የባህል ምሽት አልነበረም ያሉት አቶ ግርማይ÷ አሁን ግን አርቲስት እንየ ታከለ ይህን እውን አድርጋለች ብለዋል።

የቱሪዝም ማዕከል የሆነችውን ጎንደር ለማጉላት መሰል የባህል ምሽት ቤቶችን ለማስፋት ይሰራልም ነው ያሉት።

የእስክስታዋ ንግስት እንየ ታከለ የባህል ምሽት ቤቱ የኢትዮጵያ መልክን ይዞ እንደተሰራ ተናግራለች።

የጎንደር ከተማና የአካባቢውን ባህል ማዕከል ሆኖ ያገለግላል ያለችው አርቲስት እንየ÷ በተወለድኩበት አካባቢ የዘመናት ህልሜ በመሳካቱ ደስተኛ ነኝ ብላለች።

18 ደረጃቸውን የጠበቁ የመኝታ ክፍሎች ያሉት የባህል ምሽት ቤቱ ለ95 ወጣቶች ቋሚ የስራ ዕድል መፍጠሩ ተገልጿል።

በከተማዋ ባለአምስት ኮከብ ሆቴል የማስፋፊያ ግንባታ ፕሮጀክት በአርቲስት እንየ ታከለ እየተገነባ ስለመሆኑም ተጠቁሟል።

በምናለ አየነው

ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት፡-

YouTube www.youtube.com/@fanamediacorporation Facebook www.facebook.com/fanabroadcasting Telegram t.me/fanatelevision Website www.fanamc.com TikTok www.tiktok.com/@fana_television WhatsApp www.whatsapp.com/channel/0029VbB0dRxG8l59MUkoWR29 Amharic Entertainment YouTube www.youtube.com/@fanaentertainment Facebook www.facebook.com/wmccwaltamediaandcommunicationcorporate TikTok www.tiktok.com/@fanamc_entertainment Amharic Documentary YouTube www.youtube.com/@fanamcdocumentary በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡ ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስለሆኑ እናመሰግናለን!