ፋና ስብስብ

ተፈጥሮ የነፈገችው እግሮች ከጉዞው ያልገቱት ወጣት

By Adimasu Aragawu

June 21, 2025

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 14፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) አካል ጉዳተኝነት ወጣት ኢሞታ ቡኤሳን የሕግ ባለሙያ ከመሆን አላገደውም፡፡ በፈተናዎች ያልተበገረው ፅናቱ ከጂንካ ዩኒቨርሲቲ በሕግ ትምህርት ዘርፍ እንዲመረቅ አስችሎታል፡፡

በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል በጋሞ ዞን ተወልዶ ያደገው ወጣት ኢሞታ ቡኤሳ ከትምህርት ይልቅ ለልመና እንዲሰማራ ብዙ ጫናዎች የደረሰበት ቢሆንም በዓላማ ፅናቱ የሕግ ባለሙያ ሆኗል።

ሁለቱንም እግሮች በተፈጥሮ ያጣው ኢሞታ ገና እንደተወለደ “ገፊ” ነው በሚል አጉል ባህል የሞት ፍርድ ተበይኖበት እንደነበር ከፋና ሚዲያ ኮርፖሬሽን ጋር በነበረው ቆይታ ገልጿል፡፡

ለዛሬ ስኬቱ ወላጅ እናቱ ወይዘሮ ጎቴ ጎሎዶ ትልቅ ሚና እንደነበራቸው የሚናገረው የሕግ ምሩቅ÷ ክራንች እና ድጋፍ በማጣት በእጁና በደረቱ እየተንፏቀቀ ለረጅም ጊዜያት ትምህርት ቤት ሲመላለስ እንደነበር ያስታውሳል፡፡ ዛሬ ግን ሁሉንም ታሪክ አድርጎታል፡፡

“ትምህርት ለማንም አይጠቅምም÷ እየተባለ ጫና ይደረግበት እንደነበር ይገልጻል፡፡

“አካል ጉዳተኞች ምንም ማድረግ እንደሚችሉ እኔ ምሳሌ ነኝ” የሚለው ባለታሪካችን ከጂንካ ዩኒቨርሲቲ በሕግ ትምህርት ዘርፍ 3 ነጥብ 3 የሆነ ውጤት በማስመዝገብ ተመርቋል።

በአስጨናቂ ጉዱ

ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት፡-

YouTube www.youtube.com/@fanamediacorporation Facebook www.facebook.com/fanabroadcasting Telegram t.me/fanatelevision Website www.fanamc.com TikTok www.tiktok.com/@fana_television WhatsApp www.whatsapp.com/channel/0029VbB0dRxG8l59MUkoWR29 Amharic Entertainment YouTube www.youtube.com/@fanaentertainment Facebook www.facebook.com/wmccwaltamediaandcommunicationcorporate TikTok www.tiktok.com/@fanamc_entertainment Amharic Documentary YouTube www.youtube.com/@fanamcdocumentary በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡ ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስለሆኑ እናመሰግናለን!