ዓለምአቀፋዊ ዜና

“እስራኤልና ኢራን የተኩስ አቁም ለማድረግ ተስማምተዋል” ፕሬዚዳንት ትራምፕ

By Melaku Gedif

June 24, 2025

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 17፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) እስራኤል እና ኢራን ዘላቂ የተኩስ አቁም ለማድረግ ተስማምተዋል አሉ የአሜሪካ ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ።

ፕሬዚዳንት ትራምፕ እንዳሉት÷ እስራኤልና ኢራን ላለፉት 12 ቀናት ሲያካሄዱት የቆዩትን ጦርነት ለማቆም ስምምነት ላይ ደርሰዋል።

የኢራን ውጪ ጉዳይ ሚኒስቴር በበኩሉ ÷ እስራኤል በቴህራን ላይ የምትፈጽመውን ጥቃት ካቆመች ኢራን የተኩስ አቁም ለማድረግ ዝግጁ ናት ብሏል፡፡

ይሁን እንጂ እስራኤል እስካሁን በጉዳዩ ላይ ያለችው ነገር አለመኖሩን ቢቢሲ በዘገባው አስፍሯል፡፡

ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት፡- YouTube www.youtube.com/@fanamediacorporation Facebook FBC (Fana Broadcasting Corporate S.C.) Telegram t.me/fanatelevision Website www.fanamc.com TikTok www.tiktok.com/@fana_television WhatsApp www.whatsapp.com/channel/0029VbB0dRxG8l59MUkoWR29 Amharic Entertainment YouTube www.youtube.com/@fanaentertainment Facebook WMCC TikTok www.tiktok.com/@fanamc_entertainment Amharic Documentary YouTube www.youtube.com/@fanamcdocumentary በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡ ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስለሆኑ እናመሰግናለን!