አዲስ አበባ፣ ሰኔ 19፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) የኢትዮጵያ አረንጓዴ አሻራ መርሐ ግብር የደን ሽፋንን በማሳደግ ብዝሃ ህይወት እንዲጠበቅ ከፍተኛ አስተዋጽኦ አበርክቷል አሉ የግብርና ሚኒስትር ግርማ አመንቴ (ዶ/ር)።
የኢትዮጵያ ብዝሃ ህይወት ኢንስቲትዩት በዘርፉ የሚያከናውናቸውን ተግባራት በተመለከተ ከክልሎች ጋር ለመምከር ያዘጋጀው የውይይት መድረክ ተካሂዷል።
ግርማ አመንቴ (ዶ/ር) በዚሁ ወቅት እንዳሉት፥ ኢትዮጵያ የብዝሃ ህይወት ሀብቶች እንዳሏት ከመግለጽ ባሻገር ዘርፉ የሚያበረክተው አስተዋጽኦ ከፍተኛ በመሆኑ የሚደረገውን ጥበቃ ማጠናከር ያስፈልጋል።
አብዛኛው የብዝሃ ህይወት የሚገኘው በደን ውስጥ በመሆኑ የደን ሽፋንን ማሳደግ እንደሚገባ ነው የገለጹት።
ኢትዮጵያ በየዓመቱ እያከናወነች ያለው የአረንጓዴ አሻራ መርሐ ግብር የደን ሽፋንን በማሳደግ ብዝሃ ህይወት እንዲጠበቅ ጉልህ አስተዋጽኦ አበርክቷል ብለዋል።
የኢትዮጵያ ብዝሃ ህይወት ኢንስቲትዩት በብዝሃ ህይወት ጥበቃ ላይ እያከናወናቸው ያሉ ተግባራት አበረታች መሆናቸውን ተናግረዋል።
የብዝሃ ህይወት ጥበቃ ስራን ይበልጥ ውጤታማ ለማድረግ የክልል የግብርና ቢሮዎችና ተጠሪ ተቋማት ድርሻ ከፍተኛ በመሆኑ በቅንጅት ሊሰሩ እንደሚገባም አስገንዝበዋል።
በኃይለማርያም ተገኝ
ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
YouTube www.youtube.com/@fanamediacorporation Facebook www.facebook.com/fanabroadcasting Telegram t.me/fanatelevision Website www.fanamc.com TikTok www.tiktok.com/@fana_television WhatsApp www.whatsapp.com/channel/0029VbB0dRxG8l59MUkoWR29 Amharic Entertainment YouTube www.youtube.com/@fanaentertainment Facebook www.facebook.com/wmccwaltamediaandcommunicationcorporate TikTok www.tiktok.com/@fanamc_entertainment Amharic Documentary YouTube www.youtube.com/@fanamcdocumentary በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡ ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስለሆኑ እናመሰግናለን!