የሀገር ውስጥ ዜና

43ኛው የጉሚ በለል መድረክ እየተካሄደ ነው

By Melaku Gedif

June 27, 2025

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 20፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) 43ኛው የጉሚ በለል መድረክ “ባህላዊ ፍርድ ቤት ለማህበራዊ ፍትህ” በሚል መሪ ሃሳብ እየተካሄደ ነው፡፡

በመርሐ ግብሩ የኦሮሚያ ጠቅላይ ፍ/ቤት ፕሬዚዳንት ጋዛሊ አባሲመል፣ የኦሮሚያ ክልል ኮሙኒኬሽን ቢሮ ኃላፊ አቶ ኃይሉ አዱኛ እና ሌሎች ባለድርሻ አካላት ተገኝተዋል፡፡

አቶ ጋዛሊ አባሲመል በመድረኩ ባደረጉት ንግግር÷ በክልሉ የፍትሕ ሥርዓቱን ለማጠናከር ከባሕላዊ ፍርድ ቤቶች ጋር በቅንጅት እየተሰራ ነው ብለዋል፡፡

በክልሉ ሁለቱ የፍትሕ ሥርዓቶች በትብብርና በቅንጅት እንዲሰሩ በማድረግ ዘላቂ ሰላምን ለማስፈን እየተሰራ እንደሚገኝም አንስተዋል፡፡

አቶ ኃይሉ አዱኛ በበኩላቸው ÷ የባሕላዊ ዳኝነት ሥርዓት ለግጭት አፈታት ሒደት ከፍተኛ ሚና እንዳለው አስረድተዋል፡፡

በቀጣይ ባሕላዊ ፍርድ ቤቶችን ከዘመናዊ ፍርድ ቤቶች ጋር የማስተሳሰሩ ሥራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ተናግረዋል፡፡

በውይይት መድረኩ በባሕላዊ ፍርድ ቤቶች ጠቀሜታ ዙሪያ የተከናወኑ ጥናታዊ ጽሑፎች ቀርበው ውይይት እየተደረገባቸው ይገኛል፡፡

በጸሃይ ጉሉማ

ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት፡-

YouTube www.youtube.com/@fanamediacorporation Facebook www.facebook.com/fanabroadcasting Telegram t.me/fanatelevision Website www.fanamc.com TikTok www.tiktok.com/@fana_television WhatsApp www.whatsapp.com/channel/0029VbB0dRxG8l59MUkoWR29 Amharic Entertainment YouTube www.youtube.com/@fanaentertainment Facebook www.facebook.com/wmccwaltamediaandcommunicationcorporate TikTok www.tiktok.com/@fanamc_entertainment Amharic Documentary YouTube www.youtube.com/@fanamcdocumentary በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡ ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስለሆኑ እናመሰግናለን!