የሀገር ውስጥ ዜና

በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የ12ኛ ክፍል ተፈታኝ ተማሪዎች ወደ ፈተና ማዕከላት እየገቡ ነው

By Abiy Getahun

June 27, 2025

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 20፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የ12ኛ ክፍል ትምህርት ማጠናቀቂያ ፈተና የሚወስዱ ተማሪዎች ወደ ፈተና ማዕከላት እየገቡ ነው አለ የክልሉ ትምህርት ቢሮ።

በቢሮው የትምህርት ምዘናና ፈተና አስተዳደር ዳይሬክተር አቶ ሲሳይ ታገሰ ለፋና ዲጂታል እንደገለጹት፤ ዘንድሮ 35 ሺህ 246 የክልሉ ተማሪዎች ሀገር አቀፉን የ12ኛ ክፍል ትምህርት ማጠናቀቂያ ፈተና ይወስዳሉ።

ከሰኔ 23 ቀን 2017 ዓ.ም ጀምሮ በሀገር አቀፍ ደረጃ የሚሰጠውን ፈተና የሚወስዱ ተማሪዎች በዩኒቨርሲቲዎች ወደ ተዘጋጁ የፈተና ማዕከላት መግባት መጀመራቸውን ተናግረዋል።

ለ35 ሺህ 246 ተማሪዎች በወረቀት እና በበይነ መረብ ፈተናውን ለመስጠት የሚያስችል በቂ ዝግጅት መደረጉን ጠቁመዋል።

በበይነ መረብ ፈተና ለሚወስዱ 7 ሺህ 211 ተማሪዎች በዩኒቨርሲቲዎች እና በአዳሪ ትምህርት ቤቶች ዘጠኝ ማዕከላት መዘጋጀታቸውን ገልጸው፤ ተማሪዎቹ ስለ ፈተና አሰጣጡ ስልጠና ማግኘታቸውን አስታውሰዋል።

በወረቀት የሚፈተኑ 28 ሺህ 35 ተማሪዎች ደግሞ በአቅራቢያቸው በሚገኙ ዩኒቨርሲቲዎች ውስጥ ልምምድ አድርገዋል ብለዋል።

በወረቀት የሚፈተኑ ሁሉም ተማሪዎች ፈተውን የሚወስዱት በዩኒቨርሲቲዎች ብቻ መሆኑንም አመላክተዋል።

ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት፡-

YouTube www.youtube.com/@fanamediacorporation Facebook www.facebook.com/fanabroadcasting Telegram t.me/fanatelevision Website www.fanamc.com TikTok www.tiktok.com/@fana_television WhatsApp www.whatsapp.com/channel/0029VbB0dRxG8l59MUkoWR29 Amharic Entertainment YouTube www.youtube.com/@fanaentertainment Facebook www.facebook.com/wmccwaltamediaandcommunicationcorporate TikTok www.tiktok.com/@fanamc_entertainment Amharic Documentary YouTube www.youtube.com/@fanamcdocumentary በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡ ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስለሆኑ እናመሰግናለን!