የሀገር ውስጥ ዜና

የሀገር ሉአላዊነትን የሚያረጋግጠው አረንጓዴ አሻራ

By Abiy Getahun

June 28, 2025

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 21፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) የግብርና ሚኒስቴር የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር የምግብ ዋስትናን እና ሉአላዊነት በማረጋገጥ የሀገር ሉአላዊነትን ያረጋግጣል አለ።

በግብርና ሚኒስቴር የተፈጥሮ ሀብት ልማት ጥበቃ እና አጠቃቀም መሪ ስራ አስፈፃሚ አቶ ፋኖሴ መኮንን ለፋና ሚዲያ ኮርፖሬሽን እንደገለፁት፤ ለ7ኛ ዙር የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ከበጋ ጀምሮ ዝግጅት ተደርጓል።

በዚህም 7 ነጥብ 5 ቢሊየን ችግኝ፣ የመትከያ ስፍራ ልየታ እና ጉድጓድ ዝግጅት መደረጉን ተናግረዋል።

ዘንድሮ ከሚተከሉት ችግኞች ውስጥ 40 ከመቶ የደን ሲሆን 60 ከመቶው ደግሞ ለምግብነት የሚሆኑ ፍራፍሬ፤ የእንስሳት መኖ እና ለአፈር ለምነት የሚያገለግሉ መሆናቸውን አብራርተዋል፡፡

የአረንጓዴ አሻራ ከጎረቤት ሀገራት ጋር ያለው ዲፕሎሚሲያዊ ግንኙነት እንዲጠናከር እና አረንጓዴ ኢኮኖሚ እንዲገነባ ማድረጉንም ገልፀዋል፡፡

የዘንድሮ የአንድ ጀምበር የአረንጓዴ አሻራ ከአንድ ወር በኋላ እንደሚጀምር የጠቀሱት አቶ ፋኖሴ ሁሉም ህብረተሰብ የራሱን አስተዋጽኦ እንዲያበረክት ጠይቀዋል።

“በመትከል ማንሰራራት” በሚል መሪ ሀሳብ ዘንድሮ ለሰባተኛ ጊዜ የሚካሄደው የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር በትናንትናው ዕለት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በተገኙበት የማስጀመሪያ ሥነ ሥርዓት መካሄዱ ይታወቃል።

በአልማዝ መኮንን

ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት፡-

YouTube www.youtube.com/@fanamediacorporation Facebook www.facebook.com/fanabroadcasting Telegram t.me/fanatelevision Website www.fanamc.com TikTok www.tiktok.com/@fana_television WhatsApp www.whatsapp.com/channel/0029VbB0dRxG8l59MUkoWR29 Amharic Entertainment YouTube www.youtube.com/@fanaentertainment Facebook www.facebook.com/wmccwaltamediaandcommunicationcorporate TikTok www.tiktok.com/@fanamc_entertainment Amharic Documentary YouTube www.youtube.com/@fanamcdocumentary በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡ ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስለሆኑ እናመሰግናለን!