አዲስ አበባ፣ ሰኔ 21፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የ12ኛ ክፍል ማጠናቀቂያ ፈተና ተፈታኝ ተማሪዎች ወደ መፈተኛ ማዕከላት መግባት ጀምረዋል፡፡
ተማሪዎቹ ከሰኔ 23 ቀን 2017 ዓ.ም ጀምሮ የሚሰጠውን ፈተና ለመውሰድ ወደ ወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ፣ ጂንካ ዩኒቨርሲቲ ዲላ ዩኒቨርሲቲ እንዲሁም በአርባምንጭ ዩኒቨርሲቲ ወደ ተዘጋጁ ማዕከላት እየገቡ ነው፡፡
የክልሉ ትምህርት ቢሮ ኃላፊ ወ/ሮ ፀሐይ ወራሳ ለፋና ሚዲያ ኮርፖሬሽን እንደገለፁት፤ ተፈታኞቹ በግል፣ በመንግስት፣ በርቀት እና በመደበኛ መርሃ ግብር በ481 ተቋማት ትምህርታቸውን ሲከታተሉ ቆይተዋል።
አጠቃላይ የተፈታኞች ቁጥር 57 ሺህ 19 መሆኑን ጠቁመው፤ ፈተናው በበይነ መረብ እና በወረቀት የሚሰጥ በመሆኑ ለተማሪዎች አዲስ እንዳይሆን የተግባር ልምምዶች መደረጋቸውንም አብራርተዋል።
ተማሪዎቹ ወደ ተለያዩ አካባቢዎች በመሄድ የሚፈተኑ በመሆኑ ከመደበኛ ትምህርታቸው ጎን ለጎን የሥነ ልቦና ዝግጅት ሲያደርጉ ቆይተዋል ብለዋል።
የዘንድሮ የ12ኛ ክፍል ትምህርት ማጠናቀቂያ ፈተና ከሰኔ 23 እስከ ሐምሌ 8 ቀን 2017 ዓ.ም ድረስ ይሰጣል፡፡
በማስተዋል አሰፋ
ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
YouTube www.youtube.com/@fanamediacorporation Facebook www.facebook.com/fanabroadcasting Telegram t.me/fanatelevision Website www.fanamc.com TikTok www.tiktok.com/@fana_television WhatsApp www.whatsapp.com/channel/0029VbB0dRxG8l59MUkoWR29 Amharic Entertainment YouTube www.youtube.com/@fanaentertainment Facebook www.facebook.com/wmccwaltamediaandcommunicationcorporate TikTok www.tiktok.com/@fanamc_entertainment Amharic Documentary YouTube www.youtube.com/@fanamcdocumentary በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡ ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስለሆኑ እናመሰግናለን!