አዲስ አበባ፣ ሰኔ 21፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) የካሜሩን ዜግነት ያላቸው ጆርጅ ኤሎምቢ የአፍሪካ ኤክስፖርት ኢምፖርት (አፍሪኤግዚም) ባንክ ፕሬዚዳንት ሆነው ተመረጡ። ተመራጩ ፕሬዚዳንት የባንኩን የዳይሬክተሮች ቦርድ በሊቀመንበርነት ይመራሉ። ኢሎምቢ የተመረጡት ባንኩን ላለፉት 10 ዓመታት በፕሬዚዳንትና የዳይሬክተሮች ቦርድ ሊቀመንበር የነበሩትን ቤኔዲክት ኦራማህ (ፕ/ር) በመተካት ነው። በባንኩ ባለድርሸዎች ጠቅላላ ጉባዔ የተመረጡት ኤሎምቢ ባንኩን በምክትል ፕሬዚዳንትነት እና በተለያዩ ደረጃዎች ላለፉት 20 ዓመታት ማገልገላቸው ተገልጿል። ኤሎምቢ ከተመሠረተ 32 ዓመታት ያስቆጠረውን ባንክ ለመምራት አራተኛው ፕሬዚዳንት ሆነዋል ሲል የባንኩ መረጃ አመልክቷል።
የባንኩ ሦሰተኛ ፕሬዚዳንት ሆነው ያገለገሉት ቤኔዲክት ኦራማህ (ፕ/ር) ባንኩን ወደላቀ ደረጃ እንዲሸጋገር አድርገዋል ተብሏል።
ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
YouTube www.youtube.com/@fanamediacorporation Facebook www.facebook.com/fanabroadcasting Telegram t.me/fanatelevision Website www.fanamc.com TikTok www.tiktok.com/@fana_television WhatsApp www.whatsapp.com/channel/0029VbB0dRxG8l59MUkoWR29 Amharic Entertainment YouTube www.youtube.com/@fanaentertainment Facebook www.facebook.com/wmccwaltamediaandcommunicationcorporate TikTok www.tiktok.com/@fanamc_entertainment Amharic Documentary YouTube www.youtube.com/@fanamcdocumentary በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡ ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስለሆኑ እናመሰግናለን!