አዲስ አበባ፣ ሰኔ 24፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ሥራ አስፈፃሚ ኮሚቴ በዛሬው ዕለት ባካሄደው ስብሰባ በተለያዩ ጉዳዮች ላይ ተወያቶ ውሳኔዎችን አሳልፏል።
በዚሁም የሲዳማ ቡና ስፖርት ከለብ የታገዱ ተጫዋቾችን በማሰለፍ ያሸነፈው የኢትዮጵያ ዋንጫ በፎርፌ ተሸናፊ ሆኖ ዋንጫው ለወላይታ ድቻ ተመላሽ እንዲደረግ እና የወላይታ ድቻ ስፖርት ክለብ የኮንፌዴሬሽን ዋንጫ የ2025/26 የውድድር ዘመን ተሳታፊ እንዲሆን ውሳኔ አሳልፏል።
በተጨማሪም የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ የፋይናንስ አስተዳደር መመርያን በመተላለፍ የተወሰነባቸውን ውሳኔ መቻል ስፖርት ክለብ፣ ሀዋሳ ከተማ ስፖርት ክለብ እና ሲዳማ ቡና ስፖርት ክለቦች ከኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን መተዳደርያ ደንብ ውጪ ጉዳዩን ወደ መደበኛ ፍርድ ቤት በመውሰድ ክስ በመመስረት እና ውሳኔውን በማሳገድ እግድ የተጣለባቸው ተጫዋቾች በሦስቱ ክለቦች ተሰልፈው እንዲጫወቱ መደረጉን በመገምገም ውሳኔ ሰጥቷል።
በዚህም ሦስቱም ክለቦች የፍትህ አካላትን ውሳኔ በአስቸኳይ ተግባራዊ እንዲያደርጉ እና መሰለፍ የሌለባቸውን የታገዱ ተጫዋቾች ተጠቅመው ያጫወቷቸው ጨዋታዎችን በሙሉ በፎርፌ ተሸናፊ እንዲሆኑ እና የተጣለባቸውን የገንዘብ ቅጣት በመክፈል ሪፖርት እንዲያደርጉ ወስኗል።
ሌሎቹ 14 ክለቦች የፋይናንስ መመሪያውን ተከትለው ስለመስራታቸው ምርመራ እንዲደረግ እና ምርመራው እስከሚጠናቀቅ በፕሪሚየር ሊግ ክለቦች መካከል የሚከናወን የተጫዋቾች የዝውውር እንቅስቃሴ ታግዶ እንድቆይ ተወስኗል።
በ2018 የሊግ ውድድር በ2017 የፕሪሚየር ሊጉ ተሳታፊ የነበሩ 18 ክለቦች እና ከከፍተኛ ሊግ ያደጉ ሁለት ቡድኖችን በማካተት በ20 ክለቦች መካከል እንዲካሄድ እና በውድድር ዓመቱ አራት ክለቦች ወደ ከፍተኛ ሊግ እንዲወርዱም ነው የተወሰነው።
ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
YouTube www.youtube.com/@fanamediacorporation Facebook www.facebook.com/fanabroadcasting Telegram t.me/fanatelevision Website www.fanamc.com TikTok www.tiktok.com/@fana_television WhatsApp www.whatsapp.com/channel/0029VbB0dRxG8l59MUkoWR29 Amharic Entertainment YouTube www.youtube.com/@fanaentertainment Facebook www.facebook.com/wmccwaltamediaandcommunicationcorporate TikTok www.tiktok.com/@fanamc_entertainment Amharic Documentary YouTube www.youtube.com/@fanamcdocumentary በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡ ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስለሆኑ እናመሰግናለን!