አዲስ አበባ፣ ነሀሴ 5፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የሀገርን ደህንነት አደጋ ላይ በመጣል የመንግስትን ሚስጥር በውጭ ላለ የሽብር ቡድን አሳልፎ በመስጠትና በሀገሪቱ ሁከትና ብጥብጥ እንዲነሳ በማድረግ ወንጀል የተጠረጠሩ አምስት ተጠርጣሪዎች ፍርድ ቤት ቀርበዋል።
ተጠርጣሪዎቹም የአዲስ አባባ የህወሓት ጽህፈት ቤት የቀድሞ ሃላፊ አቶ ተወልደ ገብረጻዲቅ፣ የህግና ፍትህ ዳይሬክተር አቶ ተስፋለም ይሕደጎ እና የአቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ የደህንነት ሃላፊ አቶ አጽብሃ አለማየሁ እና ሌሎች ሁለት ግለሰቦች ናቸው።